Monday, 26 September 2016 00:00

የደ/ አፍሪካ ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች በተማሪዎች ተቃውሞ ተዘጉ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 - ተቃውሞውን ያስነሳው መንግስት የክፍያ ጭማሪ ማድረጉ ነው

     የደቡብ አፍሪካ መንግስት በመጪው አመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ክፍያ እንደሚጨምር ማስታወቁን ተከትሎ ባለፈው ማክሰኞ ተማሪዎች ባደረጉት ተቃውሞ ውድመት መድረሱንና ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኬፕታውንን ጨምሮ ሌሎች ታላላቅ የአገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች አገልግሎት መስጠት አቁመው መዘጋታቸውን ሮይተርስ ዘገበ፡፡
“መንግስት በክፍያ ላይ ጭማሪ ማድረጉ አግባብ አይደለም”፣ #ትምህርት በነጻ ሊሰጥ ይገባል” በሚል በአገሪቱ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች ተቃውሞ ማድረጋቸውንና ብጥብጥ መከሰቱን ተከትሎ በተፈጠረው የጸጥታ ስጋት ሳቢያ፣ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኬፕታውን፣ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ዘ ዊትዋተርስራንድ፣ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ፕሪቶሪያን የመሳሰሉ ተቋማት መዘጋታቸው ተነግሯል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ባለፈው ሰኞ በቀጣዩ አመት በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ክፍያ ላይ የ8 በመቶ ጭማሪ እንደሚያደርግ ማስታወቁን ያስታወሰው ዘገባው፤ይህ መግለጫ ያስቆጣቸው የአገሪቱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከፍተኛ ተቃውሞ ከማሰማት ባለፈ የዩኒቨርሲቲዎችን ንብረቶች በከፍተኛ ሁኔታ ማውደማቸውን ጠቁሟል፡፡  

Read 1071 times