Monday, 26 September 2016 00:00

በሰሜን ኮርያ አገልግሎት የሚሰጡ ድረ-ገጾች 28 ብቻ ናቸው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

    ነዋሪነቱ በአሜሪካ የሆነ አንድ የቴሌኮም ኢንጂነር ከሰሜን ኮርያ ከፍተኛ የመረጃ ተቋም ባገኘው ድንገተኛ መረጃ፣ በአገሪቱ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ድረ-ገጾች 28 ብቻ መሆናቸውን እንዳረጋገጠ ዘ ጋርዲያን ባለፈው ረቡዕ ዘግቧል፡፡
በአገሪቱ አገልግሎት በመስጠት ላይ ከሚገኙት ከእነዚህ ድረ-ገጾች አብዛኞቹ የመንግስት መስሪያ ቤቶችና በመንግስት ቁጥጥር ስር ያሉ መገናኛ ብዙሃን ናቸው ያለው ዘገባው፤ድረገጾቹ የመንግስት ፕሮፓጋንዳዎችን ከማሰራጨት ያለፈ ፋይዳ እንደሌላቸውም ገልጧል፡፡ ቢቢሲ በበኩሉ፤ ሰሜን ኮርያ ዜጎቿ የኢንተርኔት አገልግሎት እንዳይጠቀሙ መከልከሏን በመጥቀስ፣ በአገልግሎት ላይ ከሚገኙት ከእነዚሁ የአገሪቱ 28 ድረ-ገጾች መካከል አብዛኞቹ ዘገምተኛ ፍጥነት ያላቸውና ይዘታቸው ወቅቱን ጠብቆ የማይስተካከል እንደሆኑ ዘግቧል፡፡
በስራ ላይ ከሚገኙት የአገሪቱ ድረ-ገጾች መካከል አብዛኞቹ የአገሪቱን ፕሬዚዳንት ትርኪ ምርኪ የእለት ውሎዎች የሚያስነብቡ እንደሆኑ የገለጸው ዘገባው፤ሌላኛው ድረ-ገጽ ደግሞ የሰሜን ኮርያን ባህላዊ ምግቦች አዘገጃጀት የተመለከቱ መረጃዎችን የያዘ እንደሆነ አስረድቷል፡፡

Read 1083 times