ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ፣ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር፣ በኮ/ል አልኸንድሮ ዴል ባዬ ተፅፎ፣ በዶ/ር ተስፋዬ መኮንን ባይለዬኝ “ቀይ አንበሳ” በሚል በተተረጎመው መፅሐፍ ላይ ነገ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መፅሐፍት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ይካሄዳል፡፡ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህር አቶ ዮናስ አሽኔ ሲሆኑ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጋብዟል፡፡
Monday, 03 October 2016 08:22
“ቀይ አንበሳ” ላይ ነገ ውይይት ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና