Monday, 10 October 2016 07:23

የናይጄሪያው መሪ 2 አውሮፕላኖች ሊሸጡ ነው

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 አላስፈላጊ ብክነትን መቀነስ የሚል ዘመቻ የጀመረው የናይጀሪያ መንግስት፤ የአገሪቱ መሪ ሙሃመድ ቡሃሪ ከሚጠቀሙባቸው 11 ልዩ አውሮፕላኖች ውስጥ ሁለቱን ለመሸጥ መወሰኑን የፕሬዚዳንቱ ቃል አቀባይ ባለፈው ረቡዕ አስታወቁ።
የአገሪቱ መንግስት ፋልከን ሰቭንኤክስ እና ሃከር 4000 የሚል መጠሪያ ያላቸውን የፕሬዚዳንቱ ልዩ አውሮፕላኖችን እንደሚሸጥ የሚገልጽ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ማውጣቱን ቃል አቀባዩ ጋርባ ሼሁ መግለጻቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡ መንግስት ለፕሬዚዳንታዊ በረራዎች የሚደረጉ ወጪዎችን ለመቀነስ ሁለቱን አውሮፕላኖች ለመሸጥ ከመወሰኑ ባሻገር  ከተቀሩት የፕሬዚዳንቱ አውሮፕላኖች የተወሰኑትን ለአገሪቱ አየር ሃይል እንደሚሰጥም ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል፡፡ ናይጀሪያ በነዳጅ ዋጋ መቀነስና በውጭ ምንዛሬ እጥረት ሳቢያ የከፋ የኢኮኖሚ ድቀት ውስጥ መግባቷንና መንግስትም ይህንን ችግር ለመፍታት በማሰብ ከጀመራቸው እርምጃዎች ውስጥ፣ አላስፈላጊ ወጪዎችን መቀነስ አንዱ እንደሆነም ዘገባው ያስረዳል፡፡

Read 3459 times