Sunday, 16 October 2016 00:00

አይሲስ የፕሮፓጋንዳ ሃላፊው አል ፉርቃን መሞቱን አመነ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  በህይወት ካሉ የቡድኑ መስራች አባላት አንዱ ነበር

      በህይወት ካሉ ጥቂት የአይሲስ መስራች አባላትና ከፍተኛ አመራሮች አንዱ እንደሆነ የሚነገርለትና የሽብር ቡድኑ የፕሮፓጋንዳ ሃላፊ ሆኖ ሲሰራ የቆየው አቡ ሞሃመድ አል ፉርቃን መሞቱን ቡድኑ በድረ-ገጹ ባወጣው መግለጫ ማረጋገጡን ቢቢሲ ዘግቧል።
የአሜሪካ የመከላከያ ተቋም ፔንታጎን ባለፈው ወር ሶርያ ውስጥ ከምትገኘው ራቃ አቅራቢያ ባደረገው የአየር ጥቃት አቡ ሞሃመድ አል ፉርቃን መግደሉን ቢያስታውቅም፣ አይሲስ ግን ምንም አይነት ምላሽ ሳይሰጥ ቆይቶ በሳምንቱ መጀመሪያ ሞቱን ማረጋገጡን ዘገባው ገልጧል፡፡
ቡድኑ ግለሰቡ መሞቱን እንጂ መቼ፣ የትና እንዴት እንደሞተ ያለው ነገር እንደሌለ የጠቆመው ዘገባው፣ ግለሰቡ የቡድኑን እንቅስቃሴ የተመለከቱ የፕሮፓጋንዳ መረጃዎችን በማዘጋጀትና በማሰራጨት እንዲሁም የቡድኑ ልሳናት የሆኑ ድረ-ገጾችንና መጽሄቶችን በበላይነት በመምራት ይሰራ እንደነበር አስታውሷል፡፡
አቡ ሞሃመድ አል ፉርቃን የአይሲስ የአመራር አካል የሆነው የሹራ ምክር ቤት አባል እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ ቡድኑ የግለሰቡን ሞት ያረጋገጠው አንድ የአሜሪካ ተቋም የአይሲስ የፕሮፓጋንዳ ስራ እየተዳከመ መሆኑን በጥናት አረጋግጫለሁ ባለበት ወቅት መሆኑን

Read 1092 times