Sunday, 23 October 2016 00:00

የኖቤል አካዳሚ፤ ለሽልማት የመረጥኩትን አርቲስት ማግኘት አልቻልኩም አለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

- የ2016 የስነ-ጽሁፍ አሸናፊው ቦብ ዳይላን፤ በሽልማት ስነ ስርዓቱ ላይ ላይገኝ ይችላል

ባለፈው ሳምንት ታዋቂውን ድምጻዊና የዘፈን ግጥም ደራሲ ቦብ ዳይላንን የ2016 የኖቤል የስነ-ጽሁፍ ተሸላሚ አድርጎ እንደመረጠው ያስታወቀው የኖቤል አካዳሚ፤ ለግለሰቡ ሽልማቱን ስለምሰጥበት ሁኔታ ላሳውቀው ለቀናት ባፈላልገውም ላገኘው ባለመቻሌ ታክቶኝ ትቼዋለሁ ማለቱን ዘ ቴሌግራፍ ዘገበ፡፡
አካዳሚው ሽልማቱን ለቦብ ዳይላን ስለሚያበረክትበትና በመጪው ህዳር ወር ላይ ስለሚከናወነው ፕሮግራም መረጃ ለመስጠት በማሰብ ድምጻዊውን ለቀናት አፈላልጎ እንዳጣውና ተስፋ ቆርጦ ፍለጋውን እንደተወው አስታውቋል፡፡
የአካዳሚው ጸሃፊ ሳራ ዳንጁስ፤ ቢቸግራቸው ወደ አንድ የቦብ ዳይላን የቅርብ ሰው ስልክ በመደወልና ኢ-ሜይል በማድረግ መረጃ መስጠታቸውንና ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅሰው፣ከዚህ በኋላ ግን እሱን መፈለግ እንደታከታቸው ተናግረዋል፡፡ ቦብ ዳይላን በሽልማት ስነስርዓቱ ላይ መገኘት ካልፈለገ የራሱ ምርጫ ነው ብለዋል- ጸሃፊዋ፡፡  
ቦብ ዳይላን ለታላቁ የኖቤል ሽልማት መመረጡን በተመለከተ እስካሁን ድረስ በይፋ ምንም ነገር ትንፍሽ አለማለቱ ብዙዎችን ሲያነጋግር መሰንበቱን የጠቆመው ዘገባው፣ ድምጻዊው በ2000 ዓ.ም ለኦስካር ሽልማት ተመርጦ በነበረበት ወቅትም በሽልማት ስነ ስርዓቱ ላይ ሳይገኝ መቅረቱን በማስታወስ፣ በዘንድሮው የኖቤል ሽልማት ስነ ስርዓት ላይም ላይገኝ እንደሚችል አመልክቷል፡፡

Read 720 times