የቀድሞው መንግስት ም/ፕሬዚዳንት በነበሩት ኮ/ል ፍስሀ ደስታ በተፃፈው ‹‹አብዮቱና ትዝታዬ›› መፅሐፍ ላይ ከሁለት ሳምንት በፊት የመጀመሪያው ክፍል ውይይት የተደረገ ሲሆን ሁለተኛው ክፍል ነገ በወመዘክር አዳራሽ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ እናት የማስታወቂያ ድርጅት ገለፀ፡፡
ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት የታሪክ ተመራማሪው አቶ አበባው አያሌው ሲሆኑ ፍላጎት ያለው ሁሉ በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ አዘጋጁ ጋብዟል፡፡
Sunday, 23 October 2016 00:00
በ‹‹አብዮቱና ትዝታዬ›› ላይ ሁለተኛው ክፍል ውይይት ነገ ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና