በዶ/ር ጃራ ሰማ የተፃፈውና ‹‹ከሱስ የነፃ ትውልድ የመፍጠር ጥበብ›› የተሰኘ መፅሀፍ ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በመወዘክር አዳራሽ ይመረቃል። መፅሃፉ በኦሮምኛና በአማርኛ የተሰናዳ ሲሆን በዋናት ለሱሰኝነት ሊዳርጉ ስለሚችሉ ዋና ዋና ምክንያቶች፣ ሱስንና ሱሰኝነትን እንዴት መከላከል እንደሚቻል፣ ከሱሰኝነት መላቀቅ ስለሚቻልባቸው መንገዶች፣ ሱስ ሊያስይዙ ስለሚችሉ ነገነሮችና በአጠቃላይ ከሱሰኝነት ነፃ ሆኖ የሚኖርበትን መንገድ የሚያመላክትና የሚተነትን እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በአማርኛ የተዘጋጀው መፅሀፍ፤ በአራት ምዕራፎች ተከፋፍሎ፣ በ156 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን በ100 ብር እየተሸጠ ይገኛል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና