Sunday, 23 October 2016 00:00

ሰሜን ኮርያ፤ አሜሪካን በኒውክሌር ልታጠቃ እንደምትችል አስጠነቀቀች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ሰሜን ኮርያ፤ የአሜሪካ መንግስት የኒውክሌር ሃይል ደህንነቷን አደጋ ላይ የሚጥል እንቅስቃሴ የሚያደርግ ከሆነ አስቀድማ በመከላከል ላይ ያተኮረ የኒውክሌር ጥቃት ልትፈጽም እንደምትልች አንድ የአገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣን ማስጠንቀቃቸውን ኤንቢሲ ኒውስ ዘግቧል፡፡
አሜሪካ አገራችንንና መሪያችንን ለማጥቃት ያለሙ የኒውክሌር መሳሪያዎችን በድንበራችን አካባቢ አደራጅታለች፤ የምትፈጽምብንን ጥቃት ለመመከት ወደ ኋላ አንልም ብለዋል፤ሊ ዮንግ ፒል የተባሉት የሰሜን ኮርያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለስልጣን፡፡
ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሚደረጉባት ተጨማሪ ማዕቀቦችም ሆኑ የአሜሪካ ጫና ሰሜን ኮርያን የጦር መሳሪያ አቅሟን ከማጠናከር በፍጹም አይገታትም ሲሉም አስታውቀዋል፤ ባለስልጣኑ። ሰሜን ኮርያ በዚህ አመት ብቻ ለአምስት ጊዜያት ያህል የኒውክሌር ሙከራ ማድረጓን ያስታወሰው ዘገባው፤አገሪቱ በቀጣይም ሌሎች ሙከራዎችን ልታደርግ እንደምትችል ባለስልጣኑ ማስታወቃቸውንም ገልጧል፡፡ አለማቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ተቋም፤ ሰሜን ኮርያ እያስፋፋችው ያለውን የኒውክሌር ፕሮግራም እጅግ አሳሳቢ ሲል እንደተቸውም አስታውሷል፡፡

Read 4598 times