“ኦባማ የፈየደው ነገር የለም፤ ድምጼን የምሰጠው ለትራምፕ ነው”
የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ወንድም የሆኑት ማሊክ ኦባማ፤ የሪፐብሊካኑ ዕጩ ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካን ዳግም ታላቅ አገር ሊያደርጋት ይችላል ማለታቸውን ኒውዮርክ ፖስት ዘግቧል፡፡
የአሜሪካና የኬንያ ዜግነት ያላቸው ማሊክ ኦባማ፤ከወራት በፊትም፣ “ወንድሜ ባራክ ኦባማ ለአሜሪካውያንም ሆነ ለኬንያውያን ቤተሰቦቻችን ፋይዳ ያለው ነገር አልሰራም፤ ስለዚህም በቀጣዩ ምርጫ ድምጼን የምሰጠው ለዶናልድ ትራምፕ ነው” ማለታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
ትራምፕ ባለፈው ረቡዕ ከተፎካካሪያቸው ሄላሪ ክሊንተን ጋር ባደረጉት የመጨረሻ ዙር የምርጫ ክርክር ላይ እንዲገኙላቸው ከጋበዟቸው የክብር እንግዶቻቸው አንዱ እኒሁ የኦባማ ወንድም ማሊክ ኦባማ እንደነበሩ ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና