Sunday, 23 October 2016 00:00

የኦባማ ወንድም፤ ትራምፕ አሜሪካን ዳግም ታላቅ ያደርጋታል አሉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 “ኦባማ የፈየደው ነገር የለም፤ ድምጼን የምሰጠው ለትራምፕ ነው”

       የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ወንድም የሆኑት ማሊክ ኦባማ፤ የሪፐብሊካኑ ዕጩ ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካን ዳግም ታላቅ አገር ሊያደርጋት ይችላል ማለታቸውን ኒውዮርክ ፖስት ዘግቧል፡፡
የአሜሪካና የኬንያ ዜግነት ያላቸው ማሊክ ኦባማ፤ከወራት በፊትም፣ “ወንድሜ ባራክ ኦባማ ለአሜሪካውያንም ሆነ ለኬንያውያን ቤተሰቦቻችን ፋይዳ ያለው ነገር አልሰራም፤ ስለዚህም በቀጣዩ ምርጫ ድምጼን የምሰጠው ለዶናልድ ትራምፕ ነው” ማለታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
ትራምፕ ባለፈው ረቡዕ ከተፎካካሪያቸው ሄላሪ ክሊንተን ጋር ባደረጉት የመጨረሻ ዙር የምርጫ ክርክር ላይ እንዲገኙላቸው ከጋበዟቸው የክብር እንግዶቻቸው አንዱ እኒሁ የኦባማ ወንድም ማሊክ ኦባማ እንደነበሩ ታውቋል፡፡

Read 3139 times