Print this page
Sunday, 23 October 2016 00:00

ጣሊያን ሌት ተቀን በነጻ የሚጠጣ የወይን ፏፏቴ ሰራች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በመካከለኛው የጣሊያን አካባቢ የምትገኘው ካልዳሪ ዲ ኦርቶና የተባለቺው ከተማ፣ እግር የጣለው ሰው ሁሉ እንዳሻው እየጠለቀ ሌት ተቀን በነጻ የሚጠጣው የወይን ፏፏቴ ሰርታ ከሰሞኑ በአገልግሎት ላይ ማዋሏ ተነግሯል፡፡
ወደ አንድ ታዋቂ የጣሊያን የእምነት መዳረሻ በሚወስድ መንገድ ላይ ወደምትገኘው ወደዚህች ከተማ ጎራ ያለ ሰው፤ባደረሰው ሰዓት ሁሉ አምስት ሳንቲም ሳያወጣ ከጣፋጩ ቀይ ወይን እየጠለቀ መጠጣት ይችላል ብሏል፤ ሜትሮ ሰሞኑን ባወጣው ዘገባ፡፡ ከተማዋ ወይን በነጻ ማቅረብ የጀመረቺው አንድ የጣሊያን የወይን እርሻ ኩባንያና መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት፣ የእምነት መዳረሻውን አካባቢ ጠብቆ ለማቆየት በጀመሩት የጋራ ፕሮጀክት አማካይነት ነው ተብሏል፡፡
አካባቢው በየአመቱ በሺህዎች የሚቆጠሩ የእምነት መንገደኞች የሚያልፉበት ነው ያለው ዘገባው፤ ጣሊያን ከዚህ ቀደምም እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ አካባቢ ተመሳሳይ የነጻ የወይን ፏፏቴ በመክፈት አገልግሎት እንዲሰጥ አድርጋ እንደነበር አስታውሷል።

Read 2542 times
Administrator

Latest from Administrator