Saturday, 29 October 2016 12:44

“Think Out Side theBox” -በላፍቶ አርት ጋለሪ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የታዋቂው ሰዓሊ ሰይፉ አበበ ከ50 በላይ ስዕሎች ለእይታ የሚቀርብበት “Think Out Side  the Box” የተሰኘ የሥዕል አውደ ርዕይ፣ ዛሬ ከቀኑ 10፡00 ላፍቶ ሞል በሚገኘው ላፍቶ አርት ጋለሪ ይከፈታል፡፡
ለቀጣዩ አንድ ወር ለተመልካች ክፍት ሆኖ በሚቆየው በዚህ አውደ ርዕይ ለእይታ የሚቀርቡት ስዕሎች፡- የመልክአ ምድርን፣ መልክአ ሰማይንና አጠቃላይ የተፈጥሮን ውበትና ቀለም የሚያሳዩ በ3D እና 2D የተዘጋጁ ስራዎች እንደሆኑ ሰዓሊው ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡ ከዚህ ቀደም ከሌሎች ሰዓሊዎች ጋር በውጭና በአገር ውስጥ ለበርካታ ጊዜያት ሥራዎቹን በቡድን ለዕይታ ያቀረበው ሰዓሊው፤ ለብቻው ደግሞ በጣይቱ ሆቴል፣. በብሔራዊ ሙዚየም፣ በብሔራዊ ቴአትር አርት ጋለሪና በዓለም ጋለሪ ሥዕሎቹን ለተመልካች አቅርቧል፡፡ ሰዓሊ ሰይፉ በ1987 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አለ ፈለገ ሰላም የስነ ጥበብና ዲዛይን ት/ቤት የተመረቀ ሲሆን በአሁን ሰዓት ከስዕል ስራው በተጨማሪ በካክተስ የሚዘጋጀው የ“what’s out” መፅሄት ግራፊክስ ዲዛይነርና የኢትዮጵያ ሰዓሊያንና ቀራፂያን ማህበር ዋና ፀሐፊ በመሆን እያገለገለ ይገኛል፡፡

Read 965 times