በወጣት ዳንኤል ዓለሙ የተዘጋጀውና በፍቅርና በሥነ ልቦና ጉዳዮች ላይ ያነጣጠረው “ነገረ ፍቅር” የተሰኘ መፅሐፍ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ገበያ ላይ ዋለ፡፡ መፅሐፉ ስለ ማፍቀር ሀይል፣ ስለ ፍቅርና ገንዘብ፣ ከሰዎች ጋር በፍቅር ስለሚኖርበት መንገድ፣ ይቅርታ ለፍቅር ስላለው ፋይዳና ሌሎች ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች በስፋት ይዳስሳል ተብሏል፡፡
በሰባት ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ178 ገጾች የተሰናዳው መፅሐፉ፤በ49 ብር ከ60 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “ፈተናን የማሸነፍ ጥበብ”፣ “ስኬታማ የፍቅር ህይወት”፣ “ገንዘብና ጭንቀት”፣ “ራስን የመለወጥ ምስጢር”፣ እና “ይህን ያውቁ ኖሯል ቁጥር 1”፣ የተሰኙ መፅሐፍትን ለንባብ አብቅቷል፡፡
Sunday, 30 October 2016 00:00
“ነገረ ፍቅር” መፅሐፍ ገበያ ላይ ዋለ
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና