Sunday, 13 November 2016 00:00

በርካታ ኢትዮጵያውያን በየመን ለአየር ድብደባ አደጋ ተጋልጠዋል

Written by 
Rate this item
(10 votes)

    በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች የሰብዓዊ ድጋፍ ይፈልጋሉ
በየመን የሚገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የጦርነትና የአየር ድብደባዎች ሰለባ ሊሆኑ በሚችሉበት እጅግ አደገኛ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ የአለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት ትናንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
በየመን የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች፤ የሰብዓዊ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የጠቆመው መግለጫው፣ ድርጅቱ በየመን በሚካሄዱ የአየር ጥቃቶችና የምድር ጦርነቶች ሳቢያ አቋርጦት የነበረውን ስደተኞችን ወደአገራቸው የመመለስ ስራ እንደገና መጀመሩንም አስታውቋል፡፡
የድርጅቱ የጅቡቲ፣ የኢትዮጵያና የየመን ቢሮዎች በጋራ ባደረጉት እንቅስቃሴ፤ ሆዴዳ በተባለው የየመን አካባቢ የነበሩ 672 ስደተኞችን ከአካባቢው የማስወጣት ስራ መስራታቸውን የጠቆመው መግለጫው፣ ተጨማሪ 150 ስደተኞችም በትናንትናው ዕለት ጅቡቲ ይደርሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ እንደሚደረግ ገልጿል፡፡

Read 3535 times