Sunday, 13 November 2016 00:00

ዩክሬናዊው ስሙን “አይፎን 7” ብሎ አስቀየረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በዩክሬን የሚገኝ አንድ የኤሌክትሮኒክስ ኩባንያ መጠሪያ ስማቸውን አይፎን 7 ብለው ላስቀየሩ የመጀመሪያዎቹ አምስት ደምበኞቹ አዲሱን ስማርት ፎን፣አይፎን 7 እንደሚሸልም ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት፣ የመጀመሪያው ወጣት ስሙን በይፋ ማስቀየሩን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
የ20 አመቱ ዩክሬናዊ ወላጆቹ ያወጡለትን ኦሌክሳንደር ቱሪን የተባለ ስም በአይፎን 7 መቀየሩን ባለፈው አርብ ማስታወቁን ተከትሎ፣ ኩባንያው ቃል የገባለትንና 850 ዶላር የሚያወጣውን አዲሱን የአፕል ምርት አይፎን 7 ስማርት ፎን ሸልሞታል ተብሏል፡፡ወጣቱ በሚመለከተው የአገሪቱ የህግ አካል ስሙን ለማስቀየር ወጪ ያደረገው 2 ዶላር ብቻ በመሆኑ ከተሸለመው አይፎን ዋጋ አንጻር አትራፊ ነው ብሏል ዘገባው፡፡
ዩክሬናዊው ለሽልማት ብሎ ያጸደቀውን አይፎን 7 የሚለውን አዲሱን ስሙን፣ ወደፊት ወደነበረበት በመቀየር በቀድሞ ስሙ ሊጠራ እንደሚችል መናገሩን የጠቆመው ዘገባው፤ ወጣቱ ስሙን መቀየሩ ቤተሰቦቹንና ጓደኞቹን አስደንግጧል ብሏል፡፡

Read 1160 times