Sunday, 20 November 2016 00:00

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ3 ወር 4 ቢ. ብር አተረፍኩ አለ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

  ከዳያስፖራ የተላከና በሃዋላ የመጣ፣ 990 ሚ. ዶላር ተቀብያለሁ ብሏል
      የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሃምሌ እስከ መስከረም፣ 7.7 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱንና 4 ቢሊዮን ብር ማትረፉን ለአዲስ አድማስ ገለፀ። የባንክ ሂሳብ የከፈቱ ደንበኞቹ ወደ 14 ሚሊዮን እንደሚጠጉ ባንኩ ጠቅሶ፣ በሩብ ዓመት ውስጥ ተቀማጭ ሂሳብን በ7.7 ቢሊዮን ብር በማሳደግና ወደ 296.1 ቢሊዮን ብር ማድረሱን አስታውቋል፡፡
በወጪ ንግድ ከሚያካሂዳቸው ስራዎች 210 ሚ. ዶላር እንዳስገባ በሩብ ዓመት ሪፖርቱ ጠቅሶ፤ ከዳያስፖራ በሃዋላ የመጣ 990 ሚ. ዶላር እንደሰበሰበ ገልጿል - ባንኩ፡፡ በብድርና በቦንድ ሽያጭ 17.7 ቢሊዮን ብር ለተበዳሪዎች በማቅረብ፣ 12 ቢሊዮን ብር ብድር ተመላሽ አድርጌያለሁ ብሏል። 14 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት፤ ጠቅላላ የቅርንጫፍ ብዛቱን 1 ሺህ 151 ማድረሱን ሲገልፅ፤ 880ሺ ደንበኞች በሞባይል የባንክ አገልግሎት እየተጠቀሙ ናቸው ብሏል፡፡  

Read 1602 times