Sunday, 20 November 2016 00:00

እንግሊዛዊው ከሴኔጋል እስከ ብራዚል ሊዋኝ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 3 ሺህ 200 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን ርቀት በ4 ወራት ለማጠናቀቅ አቅዷል
      ቤን ሆፐር የተባለው እንግሊዛዊ ከሴኔጋል በመነሳት አትላንቲክ ውቅያኖስን አቋርጦ ብራዚል የሚደርሰውንና 3 ሺህ 200 ኪሎሜትር የሚሸፍነውን የውሃ ዋና ባለፈው እሁድ መጀመሩን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
የ38 አመቱ እንግሊዛዊ ረጅም ርቀት የሚሸፍነውን የውሃ ዋና ለማድረግ ከ3 አመታት በላይ መዘጋጀቱን የጠቆመው ዘገባው፣ ዋናውን ለማጠናቀቅ አራት ወራት ያህል ጊዜ ይፈጅበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጧል፡፡ ሆፐር ዋናውን በሰላም ካጠናቀቀ አንድን ውቅያኖስ አቋርጦ ከአንድ አህጉር ወደሌላ አህጉር ረጅም ዋና በማድረግ በአለም የክብረ ወሰን መዝገብ እንደሚሰፍር የጠቆመው ዘገባው፣ ዋናተኛውን ሁለት ጀልባዎች እንደሚከተሉት አመልክቷል፡፡
የቀድሞ የእንግሊዝ የፖሊስ መኮንን የነበረው ሆፐር፤ በቀን ለ12 ሰዓት ያህል በመዋኘት ረጅሙን ርቀት ለማጠናቀቅ ማቀዱ የተነገረ ሲሆን፣ በዋናው የገቢ ማሰባሰቢያ በማድረግ 1 ሚሊዮን ዶላር ለግብረ ሰናይ ድርጅቶች ለመለገስ ማሰቡም ተዘግቧል፡፡

Read 890 times