ከአምስት ዓመት በፊት በሌላ የቴሌቪዥን ጣቢያ ይተላለፍ የነበረው ‹‹ሀበሻ ዊክሊ ቲቪ ሾው›› በጄቲቪ መቅረብ ጀመረ፡፡ የቴሌቪዥን ፕሮግራሙ፡- ‹‹ሀበሻ እይታ››፣ ‹‹የሀበሻ ጊዜ››፣ ‹‹ነጭ ወረቀት›› የተሰኙና ሌሎችም አዝናኝና መረጃ ሰጪ ዝግጅቶች ይስተናገዱበታል ተብሏል፡፡ ፕሮግራሙ በተጨማሪም የአማርኛ ፊልሞች፣ ሙዚቃዎችና ልዩ የኪነ ጥበብ መሰናዶዎች እንደሚቀርቡበት የ‹‹ሀበሻ ዊክሊ›› አዘጋጆች አቶ አዶኒክ ወርቁና ወ/ሮ ሀና ኢተቻ የገለፁ ሲሆን ፕሮግራሙ ዘወትር እሁድ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ ለተመልካች እንደሚቀርብም ታውቋል፡፡
Saturday, 19 November 2016 12:07
“ሀበሻ ዊክሊ ቲቪ ሾው” በጄቲቪ መቅረብ ጀመረ
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና