Sunday, 27 November 2016 00:00

“ስፔስኤክስ” ከ4 ሺህ በላይ ሳተላይቶችን ለማምጠቅ አቅዷል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ታዋቂው የግል የኤሮስፔስ ኩባንያ ስፔስኤክስ መሰረቱን በህዋ ላይ ያደረገ አለማቀፍ የኢንተርኔት አገልግሎት ለመዘርጋት የሚያስቸሉ ከ4 ሺህ በላይ ሳተላይቶችን ለማምጠቅ ማቀዱን አስታውቋል፡፡ ኩባንያው እቅዱን ለማሳካት የሚያስችሉትን 4
ሺህ 425 ሳተላይቶች የማምጠቅ ፈቃድ እንዲሰጠው ለአሜሪካ መንግስት ጥያቄ ማቅረቡን የዘገበው ዘ ዴይሊ ሚረር፣ የኩባንያው እቅድ የሚሳካ ከሆነ በየትኛውም የአለማችን ክፍል የሚገኝ ሰው የፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ ሊሆን እንደሚችል ገልጧል፡፡ የኩባንያው የህዋ የኢንተርኔት አገልግሎት ፍጥነት እስከ 23 ጊጋ ባይት በሰከንድ እንደሚደርስ የጠቆመው ዘገባው፣ ፕሮጀክቱ 10 ቢሊዮን ዶላር ያህል ወጪ እንደሚደረግበት የኩባንያው ባለቤት ከዚህ ቀደም ማስታወቃቸውን አስታውሷል፡፡
ስፔስኤክስ የመጀመሪያውን ሳተላይት የሚያመጥቅበትን ትክክለኛ ጊዜ አለመግለጹን የገለጸው ዘገባው፣ ሳተላይቶቹ ወደ ጠፈር በተላኩ ከአምስት እስከ 7 ቸመታት ጊዜ በአገልግሎት ላይ እንደሚቆዩ አስረድቷል፡፡ በአሁኑ ሰአት ምድርን በመዞር ላይ የሚገኙ ስራ ያላቋረጡ ሳተላይቶች ቁጥር 1 ሺህ 419 ያህል እንደሆነም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1169 times