Sunday, 27 November 2016 00:00

የቱርክ መንግስት ተጨማሪ 15 ሺህ የመንግስት ሰራተኞችን አባረረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በ4 ወራት ጊዜ ከስራ የተባረሩ 125 ሺህ፣ የታሰሩ 36 ሺህ ደርሰዋል

ባለፈው ሃምሌ ወር ከተቃጣበት የከሸፈ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጋር በተያያዘ በርካታ  ዜጎቹን በማሰርና ከስራ ገበታቸው በማፈናቀል ተጠምዶ የከረመው የቱርክ መንግስት፣ ተጨማሪ ከ15 ሺህ በላይ የመንግስት ሰራተኞችን ማባረሩን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡የአገሪቱ መንግስት ባለፈው ማክሰኞ በወሰደው እርምጃ ከስራ ገበታቸው የተፈናቀሉት እነዚሁ ቱርካውያን በውትድርና፣ በፖሊስ፣ በግብር ምርመራና በሌሎች የስራ መስኮች ላይ የተሰማሩ ናቸው ያለው ዘገባው፣ ይህም ከሃምሌ ወዲህ ከስራ የተፈናቀሉና የታገዱ ዜጎችን ቁጥር ከ125 ሺህ በላይ እንዳደረሰው ገልጧል፡፡ከመፈንቅለ መንግስቱ ጋር ንክኪ አላችሁ በሚል
በአገሪቱ መንግስት የታሰሩ ዜጎች ቁጥር 36 ሺህ ያህል እንደሚደርስ የጠቆመው ዘገባው፣ መንግስት መሰልእርምጃ መውሰዱን እንደሚቀጥል ማስታወቁንም አብራርቷል፡፡ በተያያዘ ዜናም የቱርኩ መሪ ጠይብ ኤርዶጋን ተመራጩን የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን አምባገነን ናቸው ሲሉ የሚተቹትን ጸረ- ዲሞክራሲ ናቸው በማለት ማውገዛቸው ተዘግቧል፡፡

Read 1172 times