Monday, 05 December 2016 09:22

ግማሹ የማእከላዊ አፍሪካ ህዝብ እርዳታ ይፈልጋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 500 ሺ ያህል ህዝብ በጦርነት አገሩን ጥሎ ተሰዷል
       የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በእርስ በእርስ ግጭት ከምትታመሰዋ የማእከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ አጠቃላይ የህዝብ ቁጥር ግማሽ ያህሉን የሚሸፍነውና ከ2 ሚሊዮን በላይ የሚሆነው የአገሪቱ ህዝብ የሰብአዊ እርዳታ እንደሚያስፈልገው አስታወቀ፡፡ አገሪቱን ከ3 አመታት በፊት ከገባችበት የእርስ በእርስ ግጭት ለማውጣትና ወደ መረጋጋት ለመመለስ የሚደረገው ጥረት የተሻለ ለውጥ ቢመዘገብበትም፣ ባለፈው መስከረም ወር በተፋላሚ ሃይሎች መካከል ዳግም ግጭት መቀስቀሱን ተከትሎ የሰብዓዊ ቀውሱ መባባሱንና የእርዳታ ፍላጎቱ መጨመሩን የተመድ የሰብዓዊ ጉዳይ ትብብር ቢሮ ማስታወቁን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ በአገሪቱ በሚንቀሳቀሱ የሰብዓዊ ድርጅቶች ላይ ሳይቀር ጥቃት እየተፈጸመ መሆኑ፣ ለዜጎች እርዳታ እንዳይደርስ እንቅፋት ጥሯል ያለው ዘገባው፤ የአገሪቱን የ2017 የሰብአዊ እርዳታ ፍላጎት ለማሟላት 400 ሚሊዮን ዶላር  ገንዘብ እንደሚያስፈልግ መገለጹንም ጠቁሟል፡፡
በአገሪቱ ለሶስት አመታት በዘለቀው የእርስ በእርስ ግጭት ሳቢያ 400 ሺህ ያህል ዜጎች በአገር ውስጥ ሲፈናቀሉ፣ ሌሎች ግማሽ ሚሊዮን ያህል ዜጎች ደግሞ ወደ ጎረቤት አገራት ቻድ፣ ካሜሩንና ኮንጎ መሰደዳቸውን ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 873 times