Monday, 05 December 2016 09:24

ጃፓናውያን የዓለማችንን እጅግ ፈጣን ኮምፒውተር ሊሰሩ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በሰከንድ 130 ኳድሪሊዮን ስሌቶችን የመስራት አቅም አለው ተብሏል
       የጃፓን ኮምፒውተር ሳይንስ ባለሙያዎች በዓለማችን በፍጥነቱ አቻ አይገኝለትም የተባለውንና በአንድ ሰከንድ 130 ኳድሪሊዮን ስሌቶችን የመስራት አቅም ያለውን እጅግ ፈጣን ኮምፒውተር ለመስራት ማቀዳቸው ተዘግቧል፡፡
139 ሚሊዮን ፓውንድ ወጪ ይደረግበታል የተባለውና ስራው በመጪው የፈረንጆች አመት 2017 ይጀመራል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ ፈጣን ኮምፒውተር፤አገሪቱ ያለ አሽከርካሪ የሚንቀሳቀሱ መኪኖችንና ሮቦቶችን በአዲስ ፈር ቀዳጅ ፈጠራ ለመስራት የያዘቺውን ዕቅድ የሚያግዝ ነው መባሉን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ናሽናል ኢንስቲቲዩት ኦፍ አድቫንስድ ኢንደስትሪያል ሳይንስ ኤንድ ቴክኖሎጂ በአገሪቱ ተቋም የሚተገበረው የፈጣን ኮምፒውተር ፕሮጀክቱ፣ የጃፓን መንግስት አገሪቱን ብቃት ያላቸው ማሽነሪዎችን በማምረት ረገድ አለማቀፍ መሪነቱን ከያዙት ደቡብ ኮርያና ቻይና ጋር ተወዳዳሪ ለማድረግ የያዘው እቅድ አካል መሆኑንም ዘገባው ጠቁሟል፡፡
የጃፓኑ ኮምፒውተር በስራ ላይ ሲውል በአሁኑ ወቅት የአለማችን ፈጣን ኮምፒውተር የሆነውን የቻይናውን “ሰንዌይ ቲያሁላይት” በመተካት የቀዳሚነቱን ስፍራ ይይዛል ተብሏል፡፡

Read 1065 times