ሙሴቪኒ በበኩላቸው፤ ሚስቶቻቸውን የሚደበድቡ ወንዶችን አውግዘዋል
የኡጋንዳ ርዕሰ መዲና ካምፓላ የካቶሊክ ሊቀ ጳጳስ ኪዚቶ ሉዋንግዋ፤የአገሪቱ ሴቶች በወንዶች ላይ ድብደባ መፈጸማቸውን እንዲያቆሙ መጠየቃቸውን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
ሚፒንጊ በተባለቺው የአገሪቱ አውራጃ ከሚቀርቡ አስር የቤት ውስጥ ጥቃት አቤቱታዎች መካከል ግማሹ፣ በሚስቶቻቸው የተደበደቡ ባሎች ጉዳይ መሆኑን የአገሪቱ ፖሊስ ሪፖርት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ነው ጳጳሱ፣”ሴቶች ወንዶችን መደብደብ ያቁሙ” ሲሉ መልዕክት ያስተላለፉት ብሏል - ዴይሊ ሞኒተር፡፡ ጳጳሱ አክለውም፣”ወንዶች የቤተሰብ መሪ (ሃላፊ) እንደሆኑ አምነው መቀበል አለባቸው፤ ባሎቻቸውን መውደድና ማክበርም ይጠበቅባቸዋል” ሲሉ መናገራቸውን ዘገባው ጠቁሟል፡፡
በአንጻሩ የዩጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩሪ ሙሴቬኒ ጾታዊ ጥቃትን ለመከላከል የሚያስችል አዲስ ዘመቻ መጀመራቸውን የጠቆመው ዘገባው፤መንግስታቸው ሚስቶቻቸውን የሚደበድቡ ባሎችን እንደሚያወግዝ ማስታወቃቸውን አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል