Monday, 12 December 2016 12:29

“ጦቢያ ጃዝ” 65ኛውን የጃዝ ምሽት ያካሂዳል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 “ጦቢያ ጃዝ” 65ኛውን የግጥም በጃዝ ምሽት የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በራስ ሆቴል አዳራሽ ያካሂዳል፡፡
በዚህ ኪነ ጥበባዊ ፕሮግራም ላይ አንጋፋና ወጣት ገጣሚያን ‹‹ነፃ አውጭ›› በተባለው የሙዚቃ ባንድ ታጅበው ግጥሞቻቸውን ለታዳሚው እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡ የጥበብ ምሽቱ አዘጋጅ እናት የማስታወቂያ ስራዎች ድርጅት ለአዲስ አድማስ እንደገለጸው፤ በመድረኩ ከግጥሞች  በተጨማሪ ዲስኩርና መነባንብም ይቀርባሉ፡፡ 

Read 2269 times