Monday, 12 December 2016 12:40

የ2600 % የመድሃኒት ዋጋ ጭማሪ ያደረጉ ኩባንያዎች 112.7 ሚ. ዶላር ተቀጡ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ለገበያ በሚያቀርቡት የመድሃኒት ምርት ላይ የ2600 % የዋጋ ጭማሪ አድርገዋል የተባሉ ሁለት የአሜሪካ ኩባንያዎች፣ በድምሩ የ112.7 ሚ. ዶላር እንዲከፍሉ ባለፈው ረቡዕ በአንግሊዝ ቅጣት እንደተጣለባቸው አሶሼትድ ፕሬስ ዘገበ፡፡
ፒፋይዘር የተባለው መድሃኒት አምራች ኩባንያ እና ፍሊን ፋርማ የተባለው አከፋፋይ ኩባንያ የሚጥል በሽታ ተጠቂዎች በሚወስዱት መድሃኒት ላይ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ አድርገዋል በሚል በእንግሊዝ የገበያ ተወዳዳሪነት ባለስልጣን ክብረ ወሰን የተመዘገበበት የተባለውን የ112.7 ሚሊዮን ዶላር ቅጣት እንደተጣለባቸው ዘገባው ገልጧል፡፡
ኩባንያዎቹ እ.ኤ.አ በ2013 ኢፓኑቲን በተባለውና በእንግሊዝ ብቻ ከ48 ሺህ በላይ ታማሚዎች ይወስዱታል ተብሎ በሚገመተው በዚህ መድሃኒት ላይ የስያሜ ለውጥና እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ተጠቃሚዎችን በዝብዘዋል በሚል ነው ቅጣቱ የተጣለባቸው፡፡
ኩባንያዎቹ በወቅቱ 2.83 ፓውንድ ይሸጥ በነበረውን በዚህ መድሃኒት ዋጋ ላይ ከፍተኛ ጭማሪ በማድረግ በ67.5 ፓውንድ እንዲሸጥ ማድረጋቸው ተጠቃሚዎችን ያለአግባብ በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር እንዲያወጡ አስገድዷል መባሉን የጠቆመው ዘገባው፤ ቅጣቱን የጣለው ባለስልጣን መስሪያ ቤት ዋጋውን እንዲቀንሱ ለኩባንያዎቹ ማስጠንቀቂያ እንደሰጣቸውም አመልክቷል፡፡

Read 1073 times