Sunday, 18 December 2016 00:00

የአፍሪካ ህብረት በቀጣዩ ጉባኤ የአዲስ አበባ የጸጥታ ጉዳይ ያሳስበኛል አለ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

“መረጋጋት ተፈጥሯል፤ ጉባኤውን የሚያደናቅፍ ስጋት የለም” - መንግስት
    የአፍሪካ ህብረት በመጪው ጥር ወር በአዲስ አበባ ሊያካሂደው ያቀደው ቀጣዩ የመሪዎች ጉባኤ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁና አገሪቱ ካለችበት ሁኔታ አንጻር በሰላም የመጠናቀቁ ጉዳይ እንደሚያሳስበው ገልጧል፡፡
የህብረቱ ሊቀመንበር ዶ/ር ንኮሳዛ ድላሚኒ ዙማ፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ባለፈው ማክሰኞ በጽህፈት ቤታቸው በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ባደረጉት ውይይት፣ ቀጣዩ የመሪዎች ጉባኤ በሰላም የመጠናቀቁ ጉዳይ እንደሚያሳስባቸው የገለጹ ሲሆን፣ ሚኒስትሩ በበኩላቸው፤ አገሪቱ ወደ መረጋጋት መምጣቷን በመጥቀስ፣ የጉባኤውን ሂደት የሚያደናቅፍ ችግር ይከሰታል የሚል ስጋት አለመኖሩን እንደገለፁ ህብረቱ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
መንግስት የወጣቶችን ስራ አጥነት የመሳሰሉ ያልተፈቱ ችግሮች መፍትሄ ለመሻት በማሰብ፣ ህዝቡን ሙሉ በሙሉ ባሳተፈ መልኩ እየሰራ መሆኑንና አገሪቱ ከህብረቱ ጋር በገባቺው የአስተናጋጅነት ስምምነት መሰረት ጉባኤው በሰላምና በተረጋጋ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቃል መግባታቸውን መግለጫው አስታውቋል፡፡

Read 5644 times