Sunday, 18 December 2016 00:00

‹‹ባላገር ቃዘኖ›› ፊልም በሲዲ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የታዋቂዋ አርቲስት አዳነች ወ/ገብርኤል ታናሽ ወንድም  ሻምበል ታደሰ ወ/ገብርኤል፤ በ2001 ዓ.ም ‹‹ቃዘኖ›› በሚል ርዕስ ያሳተመውን ታሪክ ቀመስ ልብ ወለድ ‹‹ባላገር ቃዘኖ›› በሚል ርዕስ ወደ ፊልምነት የቀየረው ሲሆን በዋሴ ሪከርድስ አማካኝነት ለተመልካች ቀርቧል፡፡
ሻምበል ታደሰ ከዚህ ቀደም እህቱ አዳነች ወ/ገብርኤል ታሳትመው በነበረው ‹‹ጠብታ›› መፅሄትና አሜሪካ ይታተም በነበረው ‹‹ሳሎን ኢትዮጵያ›› ጋዜጣ ላይ በምክትል ዋና አዘጋጅነት ይሰራ እንደነበር ታውቋል፡፡
ሻምበል ታደሰ ከዚህ ቀደም ‹‹ሰዓትና ዘመን›› የተሰኘ የግጥም መድበል ለንባብ ያበቃ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በባህል ህክምና ዘርፍ በአምስት ፈጠራዎች የባለቤትነት መብትና ፈቃድ አግኝቶ፣ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ በመስራት ላይ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 701 times