ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጀት 95ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ በዛሬው ዕለት ለበጎ አድራጎ ድርጅቶች 132 ሺህ ብር የሚገመት የቁሳቁስ እርዳታ ያበረክታል፡፡
ድርጅቱ “ለቀጨኔ ሴት ህፃናት ማሳደጊያ ተቋም” እና “የወደቁትን አንሱ የአረጋውያን መርጃ ማህበር”፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት እርዳታውን ያበረክታል ተብሏል፡፡
ማተሚያ ድርጅቱ፤ ለእያንዳንዳቸው 66ሺህ ብር በመመደብ፡- 20 አልጋዎች፣ 20 ፍራሽ፣ 20 ብርድ ልብስ፣ 20 አንሶላና የትራስ ልብስ እንዲሁም ሌሎች ልዩ ልዩ ቁሳቁሶች እንደሚያበረክት አስታውቋል፡፡
Published in
ዜና