Sunday, 25 December 2016 00:00

በሰሃራ ከ37 አመታት በኋላ በረሃ በረዶ ጣለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  በሰሃራ በረሃ ውስጥ በሚገኘውና አልጀሪያንና ሞሮኮን በሚያዋስነው ተራራማ አካባቢ ከ37 አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ባለፈው ሰኞ ማለዳ ላይ ያልተጠበቀ በረዶ መጣሉን የእንግሊዙ ሜትሮ ጋዜጣ  ዘግቧል፡፡ በረዶው ለአንድ ቀን ያህል ከቆየ በኋላ መቅለጡን የጠቆመው ዘገባው ፤ በሰሃራ በረሃ በረዶ ሲጥል ይህ በታሪክ ለሁለተኛ ጊዜ እንደሆነ በማስታወስ ክስተቱ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያያዞ የመጣ ሊሆን እንደሚችል መነገሩንም ገልጧል፡፡
ከዚህ በፊት በሰሃራ በረሃ በረዶ ጥሎ የነበረው እ.ኤ.አ በ1979 ወርሃ የካቲት ላይ እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፤ በወቅቱ የጣለው በረዶ ለግማሽ ሰዓት ያህል ቆይቶ መቅለጡን በመጠቆም፣ ከዚያ ጊዜ ወዲህ ግን አንዲትም የበረዶ ቅንጣት በበረሃው ክልል ውስጥ ታይታ እንደማትታወቅም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 2264 times