በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአዕምሮ ህክምና ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰርና የትምህርት ክፍሉ ሃላፊ በሆኑት ዶ/ር ዳዊት ወንድምአገኝ ተፅፎ፣ ባለፈው ሳምንት ለንባብ የበቃው ‹‹አለመኖር›› የተሰኘ መፅሐፍ፤ ዛሬ ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ ቦሌ ሩዋንዳ በሚገኘው ባታ የባህል ምግብ አዳራሽ እንደሚመረቅ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ክላስ ፕላስ ኤቨንት አስታውቋል፡፡
በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ መፅሐፉ ለውይይት የሚቀርብ ሲሆን የአዕምሮ ሀኪሙ ዶ/ር መስፍን አርአያ፣ የፍልስፍና ምሁሩ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይና ወ/ሮ ሶሎሜ ታደሰ በመጽሐፉ ላይ ጥናታዊ ጽሁፍ እንደሚያቀርቡ ይጠበቃል፡፡