Monday, 09 January 2017 00:00

ሼህ ኑር ይማምን ገድላችኋል የተባሉ 13 ተከሳሾች ጥፋተኛ ተባሉ

Written by  ማህሌት ፋሲል
Rate this item
(0 votes)

   በደሴ ሼህ ኑር ይማምን ገድላችኋል የተባሉ ተከሳሾች ትላንትና በዋለው ችሎት ጥፋተኛ የተባሉ ሲሆን የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለጥር 9 ተቀጥረዋል፡፡  
በእነ አህመድ እንድሪስ መዝገብ ክስ የተመሰረተባቸው 12 ግለሰቦች ያቀረቡት መከላከያ በሙሉ ውድቅ የተደረገባቸው ሲሆን፤ ጉዳዩን እየመረመረ የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ችሎት፣ በትላንትናው ዕለት ጥፋተኛ ብሏቸዋል፡፡
ተከሳሾቹ መጀመሪያ 14 የነበሩ ሲሆን 9ኛው ተከሳሽ ሙባረክ ይመር፣ ጥር 5 ቀን 2008 ዓ.ም ጉዳዩን በማረሚያ ቤት ሆኖ በመከታተል ላይ ሳለ፣ በድንገተኛ ህመም ህይወቱ ማለፉ ተጠቁሟል፡፡ ተከሳሾቹ በ2004 ዓ.ም በደሴ ከተማ ታዋቂ የሃይማኖት መምህር የነበሩትን ሼህ ኑር ይማምን በጥይት መግደላቸውን ፍ/ቤቱ በማስረጃዎች ማረጋገጡን አመልክቷል፡፡
በሌላ በኩል እስላማዊ መንግስት ለመመስረትና የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን ለማስፈታት ተንቀሳቅሰዋል የተባሉት በእነ ነቢል ሲራጅ መዝገብ የተከሰሱ 7 ተከሳሾች ትናንት፤ እስከ 3 ዓመት ከ11 ወር ቅጣት ተላልፎባቸዋል፡፡  

Read 2378 times