Print this page
Sunday, 08 January 2017 00:00

‹‹በኢንተርኔት ስሜን ያጠፉትን በህግ እፋረዳለሁ››

Written by 
Rate this item
(5 votes)

በቅርቡ በኦሮሞ አባገዳዎች ም/ቤት የአባዱላነት ማዕረግ በተሰጣቸው ባለሀብቱ አቶ ድንቁ ደያስ የተቋቋመውና በስሩ 5 ድርጅቶችን ያቀፈው ‹‹ሶሩማ ፋን ቢዝነስ ግሩፕ››፤ በተለያዩ  ማህበራዊ ሚዲያዎች የስም ማጥፋት ዘመቻ እየተካሄደበት መሆኑን ገልፆ ጉዳዩን በህግ ለመፋረድ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።
ሶደሬ ሪዞርት ሆቴል፣ ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርስቲ፣ ሪፍት ቫሊ ሆስፒታል፣ ናፍያድ ት/ቤት፣ ኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ፤ ቀርሺ ማይክሮፋይናንስ የሚሉ የንግድ ድርጅቶችን በስሩ ያካተተው ቢዝነስ ግሩፑ፤ 10 ሺህ የሚደርሱ የሚደርሱ ሰራተኞችን እንደሚያስተዳድርም ተገልጿል፡፡
የቢዝነስ ግሩፑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ረታ በቀለ በፅ/ቤታቸው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ድርጅቶቹ ከመንግስት ጋር መልካም ግንኙነት ያላቸው ቢሆንም በተለይ ሶደሬ ሪዞርትና ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት እንደተዘጉ ተደርጎ የተናፈሰው ዘገባ ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀው ድርጅቶቹ መደበኛ አገልግሎታቸው እየሰጡ መሆናቸው ተናግረዋል፡፡
“ከመንግስት ጋር ጥሩ ግንኙነት አለን፣ ከቀረጥ ነፃ እቃዎችን በማስገባት ጭምር መንግስት ድጋፍ እያደረገልን ነው” ያሉት ስራ አስኪያጁ፤ የተናፈሰው ዘገባ ምንጩ እንደማይታወቅና ጉዳዩን የኩባንያው የህግ ባለሙያዎች እየመረመሩት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የድርጅቶቹ ባለቤት አቶ ድንቁ ደያስም፣ ሃገራቸውን እንዳልከዱና በውጭ ሃገር በህክምና ላይ መሠንበታቸውን ጠቁመው፣ በአሁን ወቅትም ህክምናቸውን አጠናቀው በአሜሪካ  ከሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ጋር ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርስቲ በትብብር በሚሠራበት ጉዳይ ላይ እየተመካከሩ እንደሆነ ዋና ስራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡፡
ተዘግቷል የተባለው ሶደሬ ሪዞርት ቀደም ሲል ግማሽ ድርሻው የመንግስት እንደነበር የጠቆሙት አቶ ረታ፤ በቅርቡ ባለሃብቱ ሙሉ በሙሉ ጠቅልለው መግዛታቸውንና አፈፃፀሙም እየተከናወን መሆኑን አስረድተዋል፡፡

Read 5190 times
Administrator

Latest from Administrator