Monday, 09 January 2017 00:00

ተንዳሆ ከእቅዱ 8 አመት ዘግይቶ፣ 5 እጥፍ ወጪ ፈጅቶ ተጠናቀቀ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

870 ሚሊዮን ብር ተመድቦለት፣ 5.6 ቢሊዮን ብር ፈጅቷል

በአፋር ብሄራዊ ክልል ከ11 አመታት በፊት የተጀመረውና ግንባታው በ3 አመታት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ታቅዶለት የነበረው የተንዳሆ የመስኖ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ከታቀደለት ጊዜ በ8 አመታት ዘግይቶ፣ ከተያዘለት በጀት 5 እጥፍ ያህል ፈጅቶ ተጠናቅቋል፡፡
በ1997 ዓ.ም የተጀመረው የተንዳሆ የመስኖ ግድብ ፕሮጀክት፣ ግንባታው ለ8 አመታት ከመጓተቱ በተጨማሪ፣ 870 ሚሊዮን ብር ይፈጃል ተብሎ ቢታቀድም፣ ወጪው በአምስት እጥፍ ያህል በማደግ 5.6 ቢሊዮን ብር መድረሱን የውሃ፣ የመስኖና የኤሌክትሪክ ሚኒስትር አስታውቋል፡፡
የተቋራጮች የልምድና የአቅም ማነስ፣ በፕሮጀክቱ ላይ በቂ ጥናቶች አለመደረጋቸውና ከፋይናንስ ጋር የተያያዙ ችግሮች፣ የመስኖ ግድቡ ከተያዘለት ጊዜ ዘግይቶ ለመጠናቀቁ ምክንያት መሆናቸውንም የውሃ፣ የመስኖና የኤሌክትሪክ ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ከበደ ገርባ ገልጸዋል፡፡
1.8 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ የማጠራቀምና 60 ሺህ ሄክታር መሬት የማልማት አቅም ያለው የተንዳሆ የመስኖ ግድብ፣ በአሁኑ ወቅትም 25 ሺህ ሄክታር የሸንኮራ አገዳና የ6 ሺህ አባወራዎችን የእርሻ ማሳዎች በመስኖ እያለማ እንደሚገኝም ተነግሯል፡፡

Read 5903 times