Sunday, 08 January 2017 00:00

‹‹አካል ጉዳተኝነት አለመቻል አይደለም›› የፋሺን ትርዒት ቀረበ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

‹‹አካል ጉዳተኝነት አለመቻል አይደለም›› በሚል መሪ ቃል የፋሽን ትርኢት ተካሄደ፡፡ በአካል ጉዳተኛዋ ሳባ ከድር (ሳቤላ) የተዘጋጀውና አካል ጉዳተኞች ሁሉን ማድረግ እንደሚችሉ ግንዛቤን ያስጨብጣል የተባለው የአካል ጉዳተኞች የፋሽን ትርኢት፤ ባለፈው ሳምንት በዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ተካሂዷል። የፋሽን ትርኢቱ ማየት በተሳናቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህግ ተማሪዎች፤ በአካል ጉዳተኛ ሰዓሊዎች፣ በድምፃዊያንና በሌላ ሙያ ላይ ባሉ አካል ጉዳተኞች የቀረበ ሲሆን የኔክስት ፋሽን ዲዛይን ት/ቤት ዲዛይነሮችም ስራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡
በትርኢቱ ላይ በአካል ጉዳተኝነት ላይ አተኩረው የሚሰሩ እውቅ አካል ጉዳተኛ ጋዜጠኞች ማርታ ደጀኔና ተስፋዬ ገ/ማሪያም በክብር እንግድነት የተገኙ ሲሆን፡፡ አካል ጉዳተኛዋ ወ/ሪት ሳባ ከድር ለታዳሚው ተሞክሮዋን ከማቅረቧም በተጨማሪ ራሷ ፅፋ ያዘጋጀችውን ‹‹ማስተዋል›› የተሰኘ የ8 ደቂቃ ፊልም ለእይታ አቅርባለች፡፡ በቀጣይም በአካል ጉዳተኝነት ላይ ያለውን አመለካከት ለመለወጥ ፕሮጀክቶችን ነድፋ እየተንቀሳቀሰች መሆኑን ገልፃ ለዚህ ህልሟ እውን መሆን ድጋፍ እንዲደረግላት ጠይቃለች፡፡

Read 1513 times