- ባለፀጋ ለመሆን ከፈለግህ፣ ተኝተህም ገንዘብ መስራት አለብህ፡፡
ዴቪድ ቤይሊ
- አበዳሪም ተበዳሪም አትሁን፡፡
ዊሊያም ሼክስፒር
- ገንዘብ ማስቀመጥ ስህተት ከሆነ፣ ትክክል መሆን አልፈልግም፡፡
ዊሊያም ሻትነር
- ከባለፀጎች የምወድላቸው ገንዘባቸውን ብቻ ነው፡፡
ናንሲ አስቶር
- ሀብታም ብዙ አዱኛ ያለው ሳይሆን ብዙ የሚሰጥ ሰው ነው፡፡
ኤሪክ ፍሮም
- ሀብታም የሚያደርግህ ደሞዝህ ሳይሆን የአወጣጥ ልማድህ ነው፡፡
ቻርልስ ኤ. ጃፌ
- ህይወት በዶላር ኖት ላይ መታተም የለበትም፡፡
ክሊፎድ ኦዴትስ
- የምንኖረው በወርቃማው ህግ ነው፡፡ ወርቁ ያላቸው ህጉን ያወጡታል፡፡
ቡዚ ባቫሲ
- ሴቶች ባይኖሩ ኖሮ በዓለም ላይ ያለው ገንዘብ በሙሉ ትርጉም አይኖረውም ነበር፡፡
አሪስቶትል ኦናሲስ
Published in
ንግድና ኢኮኖሚ