Print this page
Monday, 09 January 2017 00:00

የቱርክ ፓርላማ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ዳግም ለ3 ወራት አራዘመ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ባለፈው ሃምሌ የተቃጣውን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተከትሎ ተግባራዊ ያደረገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከአንድ ወር በፊት (በጥቅምት) ለ3 ወራት ያራዘመው የቱርክ ፓርላማ፤ባለፈው ማክሰኞ ባሳለፈው ውሳኔ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን እንደገና ለ3 ወራት ማራዘሙን ሮይተርስ ዘገበ፡፡
ፓርላማው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ደጋግሞ ማራዘሙ፣ የአገሪቱ መንግስት ያለ ከልካይ የዜጎችን መብቶች የሚገድቡ ወይም ሙሉ ለሙሉ የሚያሳጡ አዳዲስ ህጎችን ለማውጣትና ተግባራዊ ለማድረግ አስችሎታል ያለው ዘገባው፣ የአገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ግን፣ አዋጁን ዳግም ማራዘም ያስፈለገው የሽብርተኞች እንቅስቃሴ መቀጠሉን በማጤን ነው ብለዋል፡፡
 ከቀናት በፊት በተከበረው የፈረንጆች አዲስ ዓመት ዕለት የተከሰተው የሽብር ጥቃት 39 ያህል ቱርካውያንን ለሞት መዳረጉን ተከትሎ በአገሪቱ ከፍተኛ ውጥረትና ስጋት የተፈጠረ ሲሆን ፓርላማው በጠራው ስብሰባ፣ አዋጁን እንደገና ለማራዘም መወሰኑን ዘገባው ገልጧል፡፡
የቱርክ መንግስት በሃምሌ ወር ከተቃጣበት መፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጋር ንክኪ አላቸው በሚል ከ40 ሺህ በላይ ሰዎችን ማሰሩንና 100 ሺህ ያህል የመንግስት ሰራተኞችን ከስራ ገበታቸው ማባረሩን ያስታወሰው ዘገባው፤ የአውሮፓ ህብረት የቱርክ መንግስት ያወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተደጋጋሚ ሲተቸው እንደነበርም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1130 times
Administrator

Latest from Administrator