Monday, 09 January 2017 00:00

ባንኮክ በ2016 በብዛት በመጎብኘት ቀዳሚ ሆናለች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ከተማዋ በአመቱ በ21.5 ሚ. ሰዎች ተጎብኝታለች
      የታይላንድ ርዕሰ መዲና ባንኮክ፣ በተጠናቀቀው የፈረንጆች አመት 2016፣ በርካታ ቁጥር ባላቸው ሰዎች በመጎብኘት ከአለማችን ከተሞች የአንደኛነት ደረጃ መያዟን ፎርብስ መጽሄት ዘግቧል፡፡
በአመቱ ባንኮክን የጎበኙ ሰዎች ቁጥር 21.5 ሚሊዮን እንደደረሰ ማስተርካርድ የተባለው ተቋም ያወጣው አመታዊ ዓለማቀፍ የመዳረሻ ከተሞች ሪፖርት ማስታወቁን የጠቆመው ዘገባው፤ በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠቺው ደግሞ በ19.9 ሚሊዮን ሰዎች የተጎበኘቺው ለንደን መሆኗን አስታውቋል። የፈረንሳዩዋ መዲና ፓሪስ በአመቱ በ18 ሚሊዮን ሰዎች በመጎብኘት ከአለማችን ከተሞች የሶስተኛነት ደረጃን የያዘች ሲሆን ዱባይ በ15.27 ሚሊዮን፣ ኒውዮርክ በ12.75 ሚሊዮን፣ ሲንጋፖር በ12.11 ሚሊዮን፣ ኳላላምፑር በ12.02 ሚሊዮን፣ ኢስታምቡል በ11.95 ሚሊዮን፣ ቶክዮ በ11.70 ሚሊዮን፣ ሴኡል በ10.2 ሚሊዮን እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
በአመቱ በ3.6 ሚሊዮን ሰዎች የተጎበኘቺው የደቡብ አፍሪካዋ ጁሃንስበርግ፣ ከአፍሪካ ከተሞች በአመቱ በበርካታ ሰዎች በመጎብኘት ቀዳሚነቱን ስትይዝ፣ ካይሮ በ1.55 ሚሊዮን፣ ኬፕታውን በ1.37 ሚሊዮን ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ መያዛቸውን ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1286 times