Print this page
Monday, 09 January 2017 00:00

ሂላሪ እና 3 የአሜሪካ የቀድሞ መሪዎች በትራምፕ በዓለ ሲመት ላይ ይገኛሉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በበዓሉ ላይ የምታቀነቅነው የ16 አመቷ ድምጻዊት፣ በአልበም ሽያጭ ቀዳሚ ሆናለች

        ተሸናፊዋን የዲሞክራት ዕጩ ሂላሪ ክሊንተንን ጨምሮ ሶስት የአሜሪካ የቀድሞ ፕሬዚዳንቶች ከሁለት ሳምንት በኋላ በዋሽንግተን ዲሲ በሚከናወነው የዶናልድ ትራምፕ በዓለ ሲመት ላይ እንደሚገኙ ማረጋገጫ መስጠታቸውን ሲቢኤስ ኒውስ ዘግቧል፡፡
ሂላሪ ክሊንተንና ባለቤታቸው የቀድሞው ፕሬዚዳንት ቢል ክሊንተን ባለፈው ማክሰኞ በትራምፕ በዓለ ሲመት ላይ እንደሚገኙ ያስታወቁ ሲሆን፣ ጂሚ ካርተርና ሌላኛው የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ደብሊው ቡሽም የበዓሉ ታዳሚዎች እንደሚሆኑ ማረጋገጫ መስጠታቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡ በህይወት ከሚገኙት የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶች በትራምፕ በዓለ ሲመት ላይ የማይገኙት ብቸኛ ሰው ትልቁ ቡሽ መሆናቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ የ92 አመቱ ቡሽ በትራምፕ በዓለ ሲመት ላይ የማይገኙት በእርጅና እና በጤማ ማጣት ሳቢያ እንደሆነ ማስታወቃቸውንም አስረድቷል። በተያያዘ ዜናም በበዓለ ሲመቱ ላይ የሙዚቃ ስራዎቿን እንድታቀርብ ከአዘጋጅ ኮሚቴው ጥያቄ የቀረበላት ድምጻዊቷ ሬቢካ ፈርጉሰን፣  ግብዣውን ተቀብላ ለመዝፈን ፈቃደኛ የምትሆነው “ስትሬንጅ ፍሩት” የተሰኘውንና በአሜሪካ የሚታየውን ዘረኝነት የሚያወግዘውን የሙዚቃ ስራዋን ለማቅረብ ከተፈቀደላት ብቻ እንደሆነ አስታውቃለች፡፡
የ16 አመቷ አሜሪካዊ ድምጻዊት ጃኪ ኢቫንቾ፤በትራምፕ በዓለ ሲመት ላይ የአሜሪካን ብሄራዊ መዝሙር እንደምታቀርብ መነገሩን ተከትሎም፣ የሙዚቃ አልበም ሽያጭዋ በከፍተኛ ደረጃ ተመንድጎ፣ በአንደኝነት ደረጃ ላይ መቀመጡ ተዘግቧል፡፡ ድምጻዊቷ የትራምፕ በዓለ ሲመት ተሳታፊ መሆኗ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በስፋት የተዘገበ ሲሆን ይህን ተከትሎም፣ “ድሪም ዊዝ ሚ” እና “ኦ ሆሊ ናይት” የተሰኙት የድምጻዊቷ አልበሞች፣ በቢልቦርድ የደረጃ ሰንጠረዥ በሁለተኛ ደረጃ መቀመጣቸውንም ዘገባዎች ጠቁመዋል፡፡

Read 3220 times
Administrator

Latest from Administrator