የገጣሚ ታዲዮስ ተክሉ “የማያውቁት መልዓክ” የግጥም መድበል ነገ ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ በሰበታ ከተማ ጂም ሲኒማ አዳራሽ ይመረቃል፡፡ መድበሉ በህይወትና በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ከ40 በላይ ግጥሞችን እንዳካተተ ታውቋል፡፡ በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ አንጋፋና ወጣት ገጣሚያን ከመፅሐፉ የተመረጡ ግጥሞችንና የራሳቸውን ስራዎች ለታዳሚው ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ የግጥም መድበሉ ለገጣሚው የመጀመሪያ ስራው ሲሆን በቀጣይም “የነፍስ ዕዳ” የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብና “መልካም መንገድ” የተሰኘ ወጥ ልቦለድ ለማሳተም በዝግጅት ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡