Sunday, 22 January 2017 00:00

‹‹ፍሬ›› ፊልም ለፌስፓኮ ፊልም ፌስቲቫል ታጨ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በክንፈ ባንቡ ተፅፎ የተዘጋጀውና የፍቅር ዘውግ ያለው ‹‹ፍሬ›› ፊልም ለዘንድሮው የታላቁ አፍሪካ ፊልም ፌስቲቫል (ፌስፓኮ) መታጨቱ ተገለፀ፡፡ አንጋፋዎቹ አርቲስት ፈለቀ የማር ውሃ አበበ፣ ራሄል ግርማና ኤማ ብዙነህ በመሪ ተዋናይነት የተሳተፉበት ይህ ፊልም፤ በፊስቲቫሉ እጩ በመሆኑ መደሰቱን ደራሲና ዳይሬክተሩ ገልጿል፡፡ በዘንድሮው የፌስፓኮ ፊልም ፌስቲቫል ላይ ከአንድ ሺህ በላይ ፊልሞች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን ኢትዮጵያዊው ‹‹ፍሬ›› ፊልም ለፍጻሜ ከቀረቡት 20 ፊልሞች አንድ መሆኑ ታውቋል፡፡ በዚህ ፌስቲቫል ላይ የፕሮፌሰር ሃይሌ ገሪማ ‹‹ጤዛ›› ፊልም ከዚህ ቀደም እጩ እንደነበር የገለፀው ክንፈ ባንቡ፤ ‹‹ፍሬ›› ሁለተኛው ኢትዮጵያዊ የዘርፉ እጩ ፊልም መሆኑን ጠቁሟል፡፡
ከፌቡራሪ 25 እስከ ማርች 4, 2017 በሚካሄደው በዚህ ፌስቲቫል ላይ ለመሳተፍ የፊልሙ አዘጋጆችና ተዋንያን ወደ ቡኪናፋሶ እንደሚጓዙ ታውቋል፡፡

Read 1546 times