Monday, 30 January 2017 00:00

ቢል ጌትስ የአለም የመጀመሪያው “ትሪሊየነር” እንደሚሆኑ ይጠበቃል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 የወቅቱ የአለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ እና የማይክሮሶፍት መስራቹ አሜሪካዊው ቢሊየነር ቢል ጌትስ፣ በመጪዎቹ 25 አመታት ጊዜ ውስጥ የአለማችን የመጀመሪያው ትሪሊየነር ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አንድ የጥናት ውጤት አመለከተ፡፡
የቢልጌትስ ሃብት በፍጥነት እያደገ መሄዱ ከቢሊየነርነት ወደ ትሪሊየነርነት ያሸጋግራቸዋል ቢባልም፣ በመዝገበ ቃላት ውስጥ ግን ትሪሊየነር የሚባል ቃል እስካሁን እንዳልሰፈረ ተዘግቧል። ኦክስፋም ኢንተርናሽናል ይፋ ያደረገው ይህ የጥናት ውጤት እንደሚለው፣ እ.ኤ.አ ከ2009 አንስቶ የሃብት መጠናቸው በአማካይ በ11 በመቶ እያደገ እዚህ የደረሰው ቢል ጌትስ፣ እድገቱ በዚሁ መጠን እየጨመረ ከቀጠለ እድሜያቸው 86 አመት ሲሞላቸው፣ የአለማችን የመጀመሪያው ትሪሊየነር ይሆናሉ ተብሎ ይገመታል፡፡
እ.ኤ.አ በ2006 የቢል ጌትስ የሃብት መጠን 50 ቢሊዮን ዶላር እንደነበር የዘገበው ፎርብስ፤ በአስር አመታት ጊዜ ውስጥ የተጣራ ሃብታቸው ከፍተኛ ጭማሪ በማሳየት፣ በተጠናቀቀው የፈረንጆች አመት 2016 ላይ 84.4 ቢሊዮን ዶላር መድረሱንም ገልጧል፡፡

Read 1602 times