ኬር ማስታወቂያ እና ፕሮሞሽን ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ትያትር ጋር በመተባበር የአድዋ ድልን 116ኛ ዓመት በተለያዩ ኪነጥበባዊ ዝግጅት እንደሚያከብር አስታወቀ፡፡ ከነገ ወዲያ ከቀኑ 11 ሰዓት በትያትር ቤቱ በሚቀርበው ዝግጅት ግጥም፣ ሽለላ፣ ፉከራ፣ ቀረርቶ፣ ትያትር፣ ውዝዋዜ፣ ሥዕል፣ ፎቶግራፍ እና ፊልም በዝግጅቱ ይቀርባል፡፡ ለዝግጅቱ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የመከላከያ ሚኒስቴር፣ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር የኪነጥበብ እና የመገናኛ ብዙሃን በተጨማሪነት እንዳገዙት ኬር ገልጿል፡፡