Monday, 30 January 2017 00:00

የ“ቼምበር ማተሚያ ቤት” መስራች አቶ አስፋው ተፈራ አረፉ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ከ14 በላይ መፃህፍት አሳትመዋል
     ቼምበር ማተሚያ ቤትን የመሰረቱትና በኢትዮጵያና በአፍሪካ ታሪኮች ላይ ያተኮሩ መፃህፍትን የፃፉት እንዲሁም ለትምህርት የሚሆኑ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች የተፃፉ ከ14 በላይ መፃህፍትን ያሳተሙት አቶ
አስፋው ተፈራ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡ በኢትዮጵያ መፅሐፍ ቅዱስ ማህበር በፕሬዚዳንትነት፣ በአዲስ አበባና በምስራቅ አፍሪካ ላይንስ ክለብ በፕሬዚዳንትነት እንዲሁም በኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች ያገለገሉት አቶ አስፋው፤ ከህልፈታቸው በፊት 10 የሚደርሱ መፃህፍትን ለህትመት እያዘጋጁ እንደነበር ታውቋል፡፡ በብሔራዊ ዩኔስኮ በድርሰት ክፍል ኃላፊነት፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በህዝብ
አስተዳደር ምርምርና ክፍል ጥናት፣ እንዲሁም በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በናይጄሪያ  በኢትዮጵያ  ኤምባሲ በዲፕሎማትነት የሰሩት አቶ አስፋው፤ የኢምፔሪያል ሆቴል መስራችና ባለቤትም ነበሩ፡፡ አቶ አስፋው ተፈራ ባደረባቸው ህመም በአገር ውስጥና በውጪ አገር ህክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው፣ ሰኞ ጥር 15 ቀን 2009 ዓ.ም ያረፉ ሲሆን የቀብራቸው ሥነ ሥርዓትም ባለፈው ረቡዕ በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል፡፡ አቶ አስፋው ተፈራ ባለትዳርና የ5 ልጆች አባት ነበሩ፡፡

Read 853 times