ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ሩት ነጋ ለምርጥ መሪ ተዋናይነት ታጭታለች
ጋለሪያ ቶሞካ ለ22ኛ ጊዜ በሚያካሂደው የስዕል ትርኢት፤ “ነፃና ንፁህ” በሚል ርዕስ የሰዓሊ ይስሃቅ ሳህሌን የሥዕል ስራዎች ለእይታ አቀረበ፡፡የሥዕል ትርኢቱ በትናንትናው እለት የተከፈተ ሲሆን የህፃናትን አለምና ህይወት የሚገልፁ የተለያዩ ስዕሎች የተካተቱበት ነው ተብሏል፡፡ “እንደ ህፃናቱ አሳሳል በወፍራም መስመራት የተሰመሩ፤ በሰፋፊ ዝርግና ደማቅ ህብረ ቀለማት የተቀቡ ነፃ፣ ንፁህና የዋህ ኪነ ቅቦች ናቸው” ብለዋል ሰዓሊ እሸቱ ጥሩነህ፤ ስለ ሰዓሊው ሥራዎች ባሰፈሩት አስተያየት፡፡ “በህፃናት ዓለም ውስጥ መገኘት፣ ያንን ዓለም መተንተን፣ በህፃናት ህሊና ውስጥ የሚፈሱ ቀለማትን ማጫወት ደስ ይለኛል” የሚለው ሰአሊው፤ ከልጅነቱ ጀምሮ በኪነ ሥዕል ሙያ ራሱን ያዳበረ መሆኑ በሥዕል ትርኢቱ መግለጫ መፅሄት ላይ ተጠቁሟል።
ሰዓሊው ከዚህ ቀደም በፈረንሳይ የባህል ማዕከል፣ በብሄራዊ ሙዚየም፣ በብሄራዊ ቴአትርና በአስኒ ቤተ ሥዕል ስራዎቹን ለዕይታ ማቅረቡ ታውቋል፡፡ “ነፃና ንፁህ”፤ ለሁለት ወራት ለተመልካች ክፍት ሆኖ ይቆያል ተብሏል፡፡ ጋለሪያ ቶሞካ የሚገኘው ሳር ቤት ካናዳ ኤምባሲ ፊት ለፊት ነው፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና