Sunday, 05 February 2017 00:00

የዘላለም ጥግ

Written by 
Rate this item
(23 votes)

(ዝነኞች በመጨረሻ ሰዓታቸው)
· “እየተሸነፍኩ ነው”
   ፍራንክ ሲናትራ
· “ብዕር ለመያዝ አቅም ቢኖረኝ ኖሮ፣መሞት እንዴት ቀላልና አስደሳች ነገር እንደሆነ እፅፍ ነበር”
  ዶ/ር ዊሊያም ሃንተር
· “የምሻው ገነት መግባት ሳይሆን ሲኦል መግባት ነው፡፡ በሲኦል የጳጳሳት፣ የነገስታትና የልኡላን ጓደኞች ይኖሩኛል፡፡ በገነት ግን የኔ ቢጤዎች፣ መነኩሴዎችና ሐዋርያት ብቻ ናቸው ያሉት”
  ኒኮሎ ማኪያቬሊ (የፍሎሬንቲን ዲፕሎማትና የፖለቲካ ፈላስፋ)
· “ሞቼአለሁ ወይም ሰዓቴ ቆሟል”
  ግሮቾ ማርክስ
· “እነዚህን መነኮሳት ከአጠገቤ ዞር አድርጉልኝ”
  ኖርማን ዳግላስ
· “ነገ ይዞ የሚመጣውን አላውቅም”
  ፈርናንዶ ፔሶ (የፖርቹጊዝ ገጣሚ)
· “ከእርስዎ ጋር ለምን አወራለሁ? አሁን ከአለቃዎት ጋር ስነጋገር ነበር”
  ዊልሰን ሚዝነር (ለቄስ የተናገረው)
  (ፀሐፌ ተውኔትና የስክሪፕት ፀሐፊ)
· “ተጣልተን እንደነበር አላውቅም”
    ሔነሪ ዴቪድ ቶሪዎ (ከእግዚአብሄር ጋር ሰላም እንዲፈጥር ሲጠየቅ)
  (አሜሪካዊ ደራሲ፣ ገጣሚ፣ ፈላስፋና የታሪክ ምሁር)
· “ሁሉንም ሰው ይቅር ብያለው፡፡ ሁሉም ሰው እኔንም ይቅር እንዲለኝ እፀልያለሁ። አሁን የሚፈሰው ደሜ ለሜክሲኮ ሰላምን ያሰፍንላታል፡፡ ሜክሲኮ ለዘላለም ትኑር፤ ነፃነት ለዘላለም ይኑር”
  ማክሲሚሊያን (የሜክሲኮ ንጉስ)
· “ዝናቡ ይሰማችኋል? ዝናቡ ይሰማችኋል?”
(አውሮፕላኗ ከመከስከሱ ከደቂቃዎች በፊት)
  ጄሲካ ዱብሮፍ

Read 6982 times