Sunday, 05 February 2017 00:00

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(73 votes)

  እኛ እና እድገት
እንደ ዜናውማ ….. እንደሚናፈሰው፣
ቀድመነው ሄደናል ….. እድገትን አልፈነው፣
ግን ወሬውን ትተን ….. እውነቱን ካሰብነው፣
ለእኛ የመሰለን ….. ጥለነው የሄድነው፣
ብዙ ዙር ደርቦን ….. ከኋላ ቆሞ ነው፡፡

     የቀን ጨረቃ
ፀሐይ ከለገመች
ቀን ላይ መውጣት ትታ፣
ለጉም ለደመናው
ካሳለፈች ሰጥታ፣
ታስረክባትና
የራሷን ፈረቃ፣
ትምጣና ታድምቀው
የእኛን ቀን ጨረቃ፡፡

    እንባህን ቅመሰው
መስታወት አትሻ
ሰውም አታስመሰክር
እንባህን ቅመሰው
ለማንም ሳትነግር፡፡
ውሃ ውሃ ካለህ
የጨው ጣዕም ከሌለው
ኡኡታህን አቁም
ለቅሶህ የውሸት ነው!
        (ከገጣሚ ሳምሶን ይርሳው ጌትነት “ምልክት” የግጥም መድበል

Read 9735 times