እናት የማስታወቂያ ስራዎች ድርጅት ከጎተ ኢንስቲትዩትና ከወመዘክር ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በብሄራዊ ቤተ መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ የአንጋፋው ደራሲ ስብሃት ገ/እግዚአብሔር የፈጠራ ስራዎች በሆኑት ‹‹ሌቱም አይነጋልኝ”፣ ‹‹ትኩሳት›› እና ‹ሰባተኛው መልዓክ›› መጻህፍት ላይ ውይይት ያካሂዳል፡፡ለውይይት የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት የስነ-ፅሁፍ ባለሙያዋ ስነ-ህይወት ገዛኸኝ ሲሆኑ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጋብዘዋል፡፡
Sunday, 05 February 2017 00:00
በደራሲ ስብሀት መጻህፍት ላይ ነገ ውይይት ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና