67ኛው ግጥም በጃዝ ምሽት የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በራስ ሆቴል ይካሄዳል፡፡ አንጋፎቹ ገጣሚያን ነቢይ መኮንን፣ ተፈሪ አለሙ፣ ዶ/ር ሙሉአለም ተገኝወርቅ፣ መርድ ተስፋዬና ቤዛ ትዕዛዙ የግጥም ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን አርቲስት ሽመልስ አበራና እታፈራሁ መብራቱ አጭር ተውኔት ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ምሁር የሆኑት አቶ አበባው አያሌው ዲስኩር እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡