በሌላ በኩል ዶ/ር አቡሽ አያሌው ያዘጋጁት “አልፋና ኦሜጋ ቁጥር 2” የሥነሕዋ ሳይንስ መፅሐፍ፣ ባለፈው እሁድ የኢትዮጵያ ኅዋ ሳይንስ ማህበር የበላይ ጠባቂ አቶ ተፈራ ዋልዋ እና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት በራስ አምባ ሆቴል ተመረቀ፡፡ ስለ አልበርት አንስታይን፣ ስለ ሕዋ የሚነሱ አወዛጋቢ ጥያቄዎች እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች በተዳሰሱበት የመጽሐፍ ምረቃ ላይ ማህበሩ ባዘጋጃቸው አራት ቴሌስኮፖች የጠፈር ጉብኝት ተከናውኗል፡፡