Sunday, 12 February 2017 00:00

በአፍሪካ በየዓመቱ ከ1 ቢ. በላይ ህፃናት ለጥቃት ይጋለጣሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    በአፍሪካ በየዓመቱ ከአንድ ቢሊዮን በላይ ህፃናት የተለያዩ ጥቃቶች እንደሚደርሱባቸው የጠቆመው “ወርልድ ቪዥን” የተሰኘው አለማቀፉ ግብረ ሰናይ ድርጅት፤ የአህጉሪቱ መሪዎች ህፃናትን ከጥቃት እንዲታደጉ ጥሪ አቅርቧል፡፡ ወርልድ ቪዥን በህፃናት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለማስቆም
አገራት የበኩላቸውን እንዲወጡ ለመጠቆምና ለመቀስቀስ ሰሞኑን በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል ባዘጋጀው የውይይት ፕሮግራም ላይ በአህጉሪቱ የሚገኙ ህፃናት ከፍተኛ በደል እንደሚፈፀምባቸው በዝርዝር ተገልጿል፡፡ የጉልበት ብዝበዛ፣ ያለ እድሜ ጋብቻ፣ የሴት ልጅ ግርዛት እንዲሁም ህፃናትን ያለ እድሜያቸው ለጦርነት የማዋልና በቀጥታ የግጭት ሰለባ የመሆን አደጋዎች እንደተበራከቱ ተመልክቷል፡፡ ከ200 በላይ የሚሆኑ
ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ አመራሮች በሂልተኑ ውይይት ላይ ተገኝተው የአህጉሪቱ ህፃናት ፍዳ በሚያበቃበት ሁኔታ ላይ የመከሩ ሲሆን “የሴት ልጅ ግርዛትን በተመለከተ፣ ከዚህ በኋላ ለድርጊቱ ምንም ትዕግስት የለንም” በሚል መርህ ሁሉም ወገን ድርጊቱን እንዲቃወምና የአህጉሪቱ ሴት ህፃናት ከግርዛት እንዲድኑ ጥሪ ተላልፏል፡፡ ከኢትዮጵያ፣ ከኡጋንዳና ከደቡብ ሱዳን የተውጣጡ የህፃናት ተወካዮችም
በአቻዎቻቸው ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።

Read 1302 times